Thursday, May 14, 2015

የሁለት አመት አስተማሪ ደሞዝ ለአንድ ቀን ፌሽታ በዲሲ (የሳሞራ የኑስ የሆቴል ወጪ በአንድ ቀን)

ጀነራል ሳሞራ የኑስ፣ የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ኤታ ማጆር ሹም ናቸው። አንዳንዶች እንደዉም አገሪቷን የሚመሩት አቶ ኃይለማሪያም ሳይሆኑ እኝሁ ጀነራል ናቸው የሚሉም አሉ። ጀነራሉ በዋሽንግተን ዲሲ Mandarine Oriental Hotel እንዳረፉ ዘገባዎች ይጠቁማሉ። ጀነራሉ ለምን ወደ አሜሪካ እንደመጡ የታወቀ ነገር የለም። በዋሺንገትን ዲሲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ድህረ ገጽ ስለ ጀነራሉ ጉብኘት በድህረ ገጹ ላይ ምንም ነገር አላሰፈረም። ምናልባትም የጀነራሉን ጉብኘት የኢትዮጵያ ኤምባሲ ላያውቀዉም ይችላል። ጀነራል በግላቸው ለግል ጉዳይ መጥተዉም ይሆናል። በምርጫው ወቅት አዲስ አበባ አለመገኘታቸው ፣ ምናልባት የሕክምና ችግርም አጋጥሟቸው ሊሆን ይችላል የሚል ግምትም በአንዳንዶች ዘንድ አለ።

ሆኖም አንድ ትኩረታችንን ሊሰብ የሚገባ ትልቅ ነጥብ አለ። ጀነራሉ ያረፉበት ሆቴል እጅግ ዘመናዊና በጣም ዉድ ሆቴል ነው። ለምሳሌ ማንዳሪን ሱት የሚባለው በቀን 1295 ዶላር ( 28 ሺህ ብር ) ነው የሚከፈለው። አምባሳደር ሱት 1495 ዶላር ( 31 ሺህ ብር ) ሲሆን ኦሪየንታል ሱት ደግሞ 2500 ዶላር ( 53 ሺህ ብር) ነው።

እንደዉ አንድ ኢትዮጵያ ያለ አስተማሪ በደንብ ተከፍሎት የወር ደሞዙ 2000 ብር ቢሆን፣ ጀነራል ሳሞራ ለአንድ ቀን ዲስ ፌሽታ የሚያወጡት ቢያንስ ለሁለት አመታት የአንድ አስተማሪን ደሞዝ የሚከፍል ነው ማለት ነው።

የጀነራሉን ወጭ የኢትዮጵያ መንግስት ከፍሎ ከሆነ፣ ኤምባሲው አወቆት፣ እንግዲህ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ምን ደረጃ ላይ እንዳለች በገሃድ በድጋሚ የሚያሳየን ነው የሚሆነው።


በግላቸው ከሆነ ደግሞ ጄነራል ሳሞራ የመጡት፣ ከሁለት አመታት በላይ የአንድ አስተማሪ ደሞዝን ሊሸፍን የሚችል ገንዘብ፣ ለአንድ ቀን ሆቴል የመክፈል አቅም እንዴት ሊኖራቸው ቻለ የሚል ጥያቄ ይነሳል። ይሄም አሁን የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ለጥቂቶች ሲኦል እንደ ጀነራል ሳሞራ ላሉ በሙስና ለተጨማለቁ ዘራፊ ባለስልጣናትና መኮንኖች ግን ገነት መሆኗንም የሚያሳይ ነው።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41359

No comments:

Post a Comment