Sunday, May 24, 2015

ኢትዮጵያ – የምርጫ ቀጣና ሳይሆን የጦርነት ቀጠና እየመሰለች ነው


የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዉጥ ይፈልጋል። የዘንድሮው ምርጫ እንደ መሳሪያ በመጠቀም፣ ለዚህ ግፈኛ መንግስት ተቃዉሞዉን ይገልጻል ተብሎ ይጠበቃል። ህወሃት/ኢህአዴግ ህዝብ እንደተፋው ያውቃል። ከዚህም የተነሳ በብዙ ቦታዎች ፣ የምርጫ ጣቢያዎች ሁሉ ተዘግተዋል። እንደ አዲስ አበባ፣ ባህር ዳር ያሉ ከተሞች የጦርነት ቀጠናዎች ይምስሉ። ቁጥሩ እጅግ በጣም ብዙ የሆነው የታጠቃ ኃይል ተሰማርቷል። ቁጥራቸው እጅግ በጣም ብዙ የሆነ ኢትዮጵያዉይን እየታፈሱ ነው።


በአገር ቤት ያለው ሁኔታ እንዲህ እንዳለ ህወሃት/ኢሕአዴግ ከፍተኛ የአለም አቀፍ ተቃዉሞ ገጥሞታል። በርካታ የዉጭ ጋዜጦች ምርጫው የዉሸት እንደሆነ እየዘገቡ ነው። የአቶ ኃይለማሪያም የአልጃዚራም ቃል ምልልስ በአገዛዙ ላይ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ዉርደትን አከናንቧል። አቶ ኃይይለማሪያ የአንድ አገር መሪ ሳይሆኑ ሃሺሻ ሳያገኝ ሲቀር የሻሺሽ ሱሰኛ እንደሚሆው ፣ የሚቀጠቀጡ ዱርዬ ነበር የሚመስሉት

ሕወሃት/ኢሕአዴግ በራዲዮና ቲቪ በመዛት፣ የወታደር ብዛት በማከማቸት፣ ታንኮች በማሰማራት በ1997 እንዳደርገው የሕዝቡን ጥያቄ አፈቤ እገዛለሁ የሚል እምነት ይኖረዋል። ሆኖም 2007 እንደ 1997 አይደለም።

ይሄ በአገዛዙ ላይ የደረሰው ዉጥረትና ውርደት ፣ የሕዝብ ትግል ያመጣው ነው። ይሄ የሕዝብ የትግል መነሳሳት ደግሞ በአገራችን የነጻነት ጮራ የሚፈነጥቅበት ጊዜ ቅርብ መሆኑ የሚያሳይ ነው። በርግጥም የሕዝብ ጉልበት ያሸንፋለ። እነርሱ ጥቂቶች ናቸው። እነርሱ እስከ አሁንም የኖሩት እየከፋፈሉ ነው። እኛ ግን ሚሊዮኖች ነን። እኛ ግን ዘር፣ ኃይይማኖት ሳንለይ አንድ ሆነናል።

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41633

No comments:

Post a Comment