Tuesday, January 15, 2013

የአለም ባንክ በኢትዮጵያ የሚታየው የሙስና ደረጃ እያደገ  መምጣቱን ይፋ አደረገ

ጥር ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የአለም ባንክ በኢትዮጵያ የሚታየው የሙስና ደረጃ እያደገ መምጣቱን ይፋ አደረገ:: በተለይ የቴሌኮም ዘርፉ ለከፍተኛ ሙስና የተጋለጠ መሆኑን አስታወቀ::
ባለፈው አርብ በአለም ባንክ ይፋ የተደረገ ሪፓርት እንዳመለከተው በተለይ በግዥና በአቅርቦት ሂደቶች የሚታዩት ክፍተቶች ለሙስና አደጋ በመጋለጥ ከፍተኛውን ድርሻ መያዛቸውን ሪፓርቱ አመልክቶል::
የሀገሪቱን የሙስና መጠን ላለፉት ስድስት ወራት ሲያጠና የቆየው የአለም ባንክ በተለይ አዳዲስ የኢንቨስትመንት መስኮች ብሎ በመደባቸው
ንዑሳን ክፍሎች ውስጥ የተካተቱት ቴሌኮም፣ የኤች አይ ቪ መከላከልና ህክምና የመድሀኒት ዘርፉን ጨምሮ በሙስና ቀለበት ውስጥ የወደቁ ናቸው ብሎል::
በመሰረታዊ አገልግሎት ሰጪ ተቆማት ብሎ ባንኩ በመደባቸው ትምህርት፣ ጤና፣ ፍትህና የመሳሰሉት ተቆማት ቀላል የማይባል ሙስና የሚታይባቸው መሆኑን አጋልጦል::
ባንኩ ያፋ ባደረገው በዚ ሪፓርት ከፍተኛ ሙስና ከሚታይበት ከቴሌኮም ኢንዱስትሪ ቀጥሎ መሬትና ኮንስትራክሽን ዘርፉ በሙስና መዘፈቁን ይፋ አድርጎል::
posted By.Dawit Demelash

No comments:

Post a Comment