Tuesday, January 29, 2013

ምርጫ ቦርድ እንደተጠበቀው ተጨማሪ የመመዝገቢያ ቀን ሰጠ

ጥር ፳፩ (ሀያ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በተመዝጋቢዎች ድርቅ የተመታው መጪው የወረዳና የአካባቢ ምርጫ ምዝገባ ለሁለት ቀናት የተራዘመ ሲሆን፣ ኢህአዴግ ካድሬዎች በዩኒቨርስቲዎች ሳይቀር እየገቡ፣ ግለሰቦች እንዲመዘገቡ ካልሆነ ግን ችግር እንደሚደርስባቸው እየገለጡ ነው።
የኢሳት ምንጮች እንደገለጡት ካድሬዎቹ በዩኒቨርስቲዎች እየዞሩ ሰራተኞችን ተመዝግባችሁዋል አልተመዘገባችሁም እያሉ ሲጠይቁ ውለዋል።
የኢህአዴግ ካድሬዎች በምርጫው ያልተመዘገቡትን ” ከእኛ ጎን ናችሁ ወይስ ከአሸባሪዎች ” በማለት እያስፈራሩ እንደሚገኙ ኢሳት ያነጋገራቸው በርካታ ሰዎች መግለጻቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
33 የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ለኢህአዴግ ምርጫ አጃቢዎች አንሆንም በማለት ራሳቸውን ለማግለል መወሰናቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢህአዴግ በበኩሉ ተቃዋሚዎች በምርጫው የማይሳተፉት ጥቅም ስለማያገኙበት ነው በማለት ተቃዋሚዎች ለወሰዱት እርምጃ መልስ ሰጥቷል።
ምርጫ ቦርድ የተመዝጋቢዎች ቁጥር በእቅዱ የተቀመጠውን ያሟላ ነው በማለት ቢገልጽም ፣ ኢሳት ያገኘው መረጃ እንደሚያሳየው እስካሁን የተመዘገበው ህዝብ ከታቀደውም ከግማሽ በታች ነው።
Posted By.Dawit Demelash

No comments:

Post a Comment